Monday, September 10, 2012

ዘመነ ማቴዎስ ወንጌላዊ እና ቅዱስ ድሜጥሮስ ተካሌ ወይን



እንኳን ለዘመነ ማቴዎስ 2005 .. በሰላም አደረሳችሁ 
ዕንቁጣጣሽ
አዲሱ ዓመት የንስሐ የቅድስና የደስታ የፍስሐ የፍቅር ያድርግልን

ሐዋርያው ቅዱስ ማቴዎስ
ማቴዎስ ወንጌላዊ 
ድሜጥሮስ መስታወት ነው፡-በመስታወት ከዓይን ጉድፍ ከጥርስ እድፍ አይተው እንደሚያጸዱበት ሁሉ ባሕረ ሐሳብንም የተማረ ሰው ዓለም ከተፈጠረ ጊዜ ጀምሮ እስከ ምጽአት ድረስ የሚሆነውን ቁጥር ያውቃልና፡፡ ባሕረ ሐሳብ ማለት ቁጥር ያለው ዘመን ማለት ነው፡፡ አንድም ሐሳብ ባሕር ይለዋል ዘመን ያለው ቁጥር ሲል ነው፡፡

ድሜጥሮስ መነጽር ነው፡- መነጽር የራቀውን አቅርቦ፣ የረቀቀውን አጉልቶ፣ የተበተነውን ሰብስቦ እንዲያሳይ እርሱም የተበተኑ አጽዋማትን በዓላትን አቅርቦ ያሳያልና፡፡
ድሜጥሮስ ጎዳና ነው፡- በጎዳናው ተጉዘው ከቤት እንደሚደርሱ ሁሉ፣ ባሕረ ሓሳብም ወደ ኋላ ያለፉትን ወደፊትም የሚመጡትን አጽዋማት በዓላትን ለይቶ ያሳውቃልና፡፡

 ድሜጥሮስ ተራራ ነው፡- በተራራው ጫፍ ላይ በወጡ ጊዜ ምንጩ ሜዳው፣ ግጫው፣ ኮረብታው እንደሚታይ ሁሉ ድሜጥሮስም የአጽዋማት በዓላትን ኢየዓርግ ኢይወርድ ጠንቅቶ ጽፏልና፡፡
ድሜጥሮስ መስተገብረ ምድር (በግብርና የሚተዳደር) ነው፡-
ይህስ ጥንተ ነገሩ እንደምን ነው ቢሉ፡-