Thursday, July 18, 2013

፱ኛው ዓመታዊው የማኅበረ በዓለ ወልድ ጉባኤ ደረሰ በካልካሪ ካናዳ ዝግጅቱ ተጠናቋል


የሚሰማምይበልየተጠማም  ይምጣ የወደደም የሕይወትን ውኃ
እንዲያው ይውሰድ“ ራዕየ ዮሐንስ ፳፪፥፲፯

በሰሜን አሜሪካ አህጉረ ስብከት የማኅበረ በዓለ ወልድ ፱ኛ ዓመት መንፈሳዊ ጉባኤ በካልጋሪ ካናዳ ዝግጅቱን አጠናቆ ከመላው አሜሪካ እና ካናዳ የሚመጡትን ካህናት አባቶች፣ ዲያቆናት፣ ሰባኬያነ ወንጌል፣ ዘማሪያን እንዲሁም ምዕመናን እና ምዕመናት በመጠባበቅ ላይ ይገኛል። በዚህ ጉባኤ ላይ ከመላው አሜሪካ እና ካናዳ የሚመጡ ተጋባዥ እንግዶች እና ከተለያዩ ከተሞች በሚመጡ የማኅበሩ አባላት ለሦስት ቀናት የተዘጋጀውን ዝግጅት ለመቋደስ ነፍሳችንን በቃለ እግዚአብሔር ለማሳነጽ ብሎም በዝማሬ እግዚአብሔርን ለማገልገል በዝግጅት ላይ እንገኛለን። እርሶስ? ዝግጅትዎን አጠናቀዋል? የቀሩት ቀናት ጥቂት ቢሆኑም ለዝግጅት ግን በቂ እንደሚሆን እናምናልን። 
ከዚህ በተጨማሪ የማኅበረ በዓለ ወልድ ካናዳ ቀጠና ላለፉት ስድስት ወራት በተከታታይ በመገናኘት ዝግጅቱን ያማረ ለማድረግ እና እግዚአብሔር የሚከብርበት ጉባኤ ለማካሄድ ደፋ ቀና ሲሉ ቆይተዋል በመሆኑም በመላው ዓለም የምንገኝ ምዕመናን በዚሁ በዓል በመገኘት የበረከቱ ተካፋይ እንድንሆን የካናዳው ማኅበረ በዓለ ወልድ በታላቅ አክብሮት ይጋብዛል።
አስታውሱ: ሐምሌ ፳፩ እና ፳፪ ቀን ፳፻፭ ዓ.ም. (July 27 & 28, 2013)
               በሐመረ ኖሕ ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ቤተክርስቲያን 
       618 – 2nd Ave NE. Calgary, Canada 
ለተጨማሪ መረጃዎች በሚከተሉት ቁጥሮች ይደውሉ
403-402-7585 / 403-542-7980 / 403-975-0141
ማኅበረ በዓለ ወልድ ካናዳ

No comments:

Post a Comment