Wednesday, December 14, 2011

“አንተም ተው አንተም ተው” - አርዮስንና ቅዱስ ቄርሎስን?!

በስመ አብ ፡ ወወልድ ፡ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን፡፡
ፍቅርን አውቃለሁ በተግባርም እገልፃለሁ የሚል - - - ነገር ግን ፍቅሩ የይምሰል የዲያቢሎስ ያልሆነበት የመንፈስ ቅዱስን ፍቅር የተገነዘበ በማስተዋልም የከበረ በተዋህዶ እምነቱ የሚኮራ በእውነት ፊት ፡ በፍቅር ሽንጎ ፡ በማስተዋልም ጥበብ ዳኛ ይሁንና ይህንን ይዳኝ ፦ በሽንጎው ላይ  ቅዱስ ቄርሎስና አርዮስ ቆመዋል፡፡ ስለጥንተ ነገራቸው፦

1)     አርዮስ የክርስቶስን አምላክነት የሚጠራጠር በተዋህዶ የምታምን ቤተክርስቲያንንም በአዲስ ትምህርት ለመለወጥ የሚተጋ ሲሆን ከአንድም ብዙ ጊዜ ትምህርቱ ስህተት እንደሆነ ሊቃውንቱ በመፅሃፍ ቅዱስ አስረጅነት በመንፈስ ቅዱስ ምስክርነት ቢያስረዱትና ቢመክሩት እምቢ ያለ ፡ ክርስቶስን ከአብ አንድነት የለየ ሲሆን ፡ ቤተክርስቲያን በዚህ እምነቱ ከአንዴም ሁለት ሶስት ጊዜ ብትለየውም አርዮስ ግን በገንዘብ የሚታለሉትን ካህናት ፡ ባለማስተዋል የሚሄዱትን ምእመናንና አለማዊ ነገስታትን በትምህርቱና በወቅቱ በነበረው የግጥም ፡ የዜማና የስነፅሁፍ እውቀት ደጋፊ አድርጎ ከአንድም ሁለት ሶስት ጊዜ ተፅፅቻለሁ እያለ ወደ መቅደስ ይገባ የነበረ ነው፡፡ ይቅርታንም ካገኝ በኅላ ምንፍቅናውንና በልቡ ያደረ ሰይጣንን ከራሱ ሊያስወግድ አልፈቀደምና መልሶ መላልሶ ወደቀደመ ክህደቱ የሚመላለስ ነው፡፡ ትምህርቱ ይህ ሲሆን ህይወቱ ደግሞ በቀደመው እድሜው የቤተክርስቲያን ዲያቆን በነበረበት የወጣትነት ጊዜ በዘመኑ የነበሩ የአህዛብ ነገስታት ቤተክርስቲያናት ወደ ጣኦትነት እንዲቀየሩ የቤተክርስቲያን ካህናትም የጣኦት ካህናት እንዲሆኑ ሲታዘዝ እውነተኞቹ ካህናት ገሚሱ ሰማእት ሲሆን ገሚሱ ሲሰደድ አንዳንዶች ግን የክርስቶስን ቤተመቅደስ እጣን ባጠኑበት እጃቸው ቅዱስ ወንጌሉን ባስተማሩበት አፋቸው ሰማእትነት ርቋቸው ፡ መፅናት አቅቷቸው ፡ የመንፈስ ፍሬ ታጥቶባቸው  ነበርና የጣኦት አገልጋይ ለመሆን አላፈሩም፡፡ ከነዚህ ውስጥ አንዱ አርዮስ ነበር፡፡ 

Monday, November 21, 2011

በዓለ ሲመቱ ለሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል

በዓለ ሲመቱ ለሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል አትም ኢሜይል
ዲ/ን ሽመልስ መርጊያ
ህዳር 11/2004 ዓ.ም

"በዚያም ዘመን ስለ ሕዝብህ ልጆች የሚቆመው ታላቁ አለቃ ሚካኤል ይነሣል ሕዝብም ከሆነ ጀምሮ እስከዚያ ዘመን ድረስ እንደ እርሱ ያለ ያልሆነ የመከራ ዘመን ይሆናል በዚያም ዘመን በመጽሐፉ ተጽፎ የተገኘው ሕዝብህ ሁሉ እያንዳንዱ ይድናል።"
ትንቢተ ዳንኤል ፲፪ ፥ ፩

mikealeየሰው ልጅ በገነት እንደ ቅዱሳን መላእክት በቅድስና አምላኩን በማመስገን በደስታ ይኖር ነበር ፡፡ ነገር ግን “ክፉና ደጉን ከምታሳውቀው ዕፀ በለስ እንዳትበላ” ተብሎ የተሰጠውን ትእዛዝ በመተላለፉ ምክንያት ከአምላኩ ተለየ(ዘፍ.3፡6) ፡፡እግዚአብሔር በአርአያውና በአምሳሉ የፈጠረው ሰው ክብሩን አጣ፣ ጸጋው ተገፈፈ ፣ ፈጣሪውንም አሳዘነ ፡፡ ቅዱሳን መላእክትም በእግዚአብሔር መልክና ምሳሌ የተፈጠረው ሰው ከክብሩ ተዋርዶ ሲመለከቱ ተከዙ ፡፡

የሰው ልጅ ጠፍቶ እንዲቀር ያልወደደው እግዚአብሔር ወልድ ሰውን ለማዳን ራሱን ዝቅ አድርጎ ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሱዋ ነፍስ ነስቶ ተወለደ ፡፡ቅዱሳን መላእክትም ከላይ ከአርያም ከአባቱ ሳይለይ እግዚአብሔር ወልድ ሰውን ለማዳን ሲል በግዕዘ ሕፃናት ተወልዶ ፣በእናቱም እቅፍ ሆኖ ፤ እንስሳት እስትንፋሳቸውን እያሟሟቁት በማየታቸው ተደነቁ ፡፡ሰውን ለማዳን ሲል ራሱን ዝቅ በማድረግ የባርያውን አርአያ እንደነሣ አስተውለው “ስብሐት ለእግዚአብሔር በሰማያት፣ ወሰላም በምድር ሥምረቱ ለሰብእ”(ሉቃ.2፡14) ብለው አመሰገኑት ፡፡

Saturday, November 19, 2011

ዘመነ ጽጌ

«ድንግል ሆይ ርጉም በሆነ ሄሮድስ ዘመን ከልጅሽ ጋር ከሀገር ሀገር ስትሸሺ ከአንቺ ጋር መሰደዱን አሳስቢ ፤
ድንግል ሆይ ከዓይንሸ የፈሰሰውንና በተወደደ ልጅሽ ፊት የወረደውን መሪር እንባ አሳስቢ፤ 
ድንግል ሆይ ረሐቡንና ጥሙን፣ ችግሩንና ሐዘኑን፣ ከእርሱ ጋር የደረሰብሽንም ጭንቅ ሁሉ አሳስቢ››
ቅዳሴ ማርያም

ጽጌ ማለት አበባ ማለት ሲሆን ዘመነ ጽጌ ማለት የአበባ ዘመን ማለት ነው፡፡በሀገራችን መስከረም 25 ቀን ዘመነ ክረምት አልፎ መስከረም 26 ቀን ዘመነ ጽጌ ይጀምራል፡፡ ዘመኑ አበቦች የሚያብቡበትና ሜዳዎችንና ተራሮችን ሚያስጌጡበት ዘመን ነው፡፡ ፍሬ የተባለ ጌታን ያስገኘች እመቤታችን በአበባ ትመሰላለችና ዘመኑ የጌታንና የእመቤታችንን ነገር በአበባና በፍሬ ለመመሰል የተመቸ ነው፡፡ስለዚህም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ከመስከረም 26 ቀን ጀምሮ እስከ ኅዳር 6 ቀን ድረስ የጌታን እና የእመቤታችን ስደት ታስባለች፡፡ በዚህ ዘመን ቅዱስ ያሬድ እና አባ ጽጌ ድንግል ባዘጋጇቸው ድርሰቶች የጌታችን እና የእመቤታችን ስደት በማኅሌት ይታሰባል፤ ምስጋና እና ልመና ይቀርባል። ምእመናን ቤተክርስቲያናቸው በሠራችላቸው ሥርዓት መሠረት በፍቅርና በደስታ ይዘክሩታል ፡፡ከዚህም በተጨማሪ ስደቱን ለማሰብና በረከት ለማግኘት በርካታ ክርስቲያኖች የአዋጅ ጾም ባይሆንም በፈቃደኝነት ዘመኑን በጾም ያሳልፉታል፡፡

Friday, November 18, 2011

ወነበረ በየማነ አቡሁ ዳግመ ይመጽዕ በስብሓት ይኮንን ህያዋነ ወሙታነ ወአልቦ ማህለቅት ለመንግስቱ

ወነበረ በየማነ አቡሁ ዳግመ ይመጽዕ በስብሓት ይኮንን ህያዋነ ወሙታነ ወአልቦ ማህለቅት ለመንግስቱ::+++

by Zema Abb Yaread የፌስ ቡክ ፔጅ የተገኘ:
 
ወነበረ በየማነ አቡሁ ዳግመ ይመጽዕ በስብሓት ይኮንን ህያዋነ ወሙታነ ወአልቦ ማህለቅት ለመንግስቱ::
እግዚአብሔር እሰ ገሃደ ይመጽዕ ወአምላክነሂ ኢያረምም እሳት ይነድድ ቅድሜሁ:: ጌታ ኢየሱስ ከሥልጣኑ መላእክት ጋር ከሰማይ በእሳት ነበልባል ሲገለጥ ፥ መከራን ለሚያሳዩአችሁ መከራን፥ መከራንም ለምትቀበሉ ከእኛ ጋር ዕረፍትን ብድራት አድርጎ እንዲመልስ በእግዚአብሔር ፊት በእርግጥ ጽድቅ ነውና።
 
እግዚአብሔርን የማያውቁትን፥ ለጌታችንም ለኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌል የማይታዘዙትን ይበቀላል ፤  በዚያም ቀን በቅዱሳኑ ሊከብር፥ ምስክርነታችንንም አምናችኋልና በሚያምኑት ሁሉ ዘንድ ሊገረም ሲመጣ ፥ ከጌታ ፊት ከኃይሉም ክብር ርቀው በዘላለም ጥፋት ይቀጣሉ።

Tuesday, November 15, 2011

ርትዕት ይእቲ ሃይማኖቶሙ ለቅዱሳን አበዊነ

«ርትዕት ይእቲ ሃይማኖቶሙ ለቅዱሳን አበዊነ ( የአባቶቻችን ሃይማኖት የቀናች ናት)»፡፡
ከማኅበረ ቅዱሳን ድረ ገጽ የተገኘ
አትም ኢሜይል

የንግግርና ሥነ ጽሕፈት ሙያን የተካኑ ምሁራን በትምህርት ጌጣቸው እንደሚሉት «ውሃን ከጥሩው ሲቀዱት፣ ነገርን ከሥሩ ሲያመጡት» ውሃው ጠጭውን፣ ነገሩም ሰሚውን ያረካዋል፡፡ በዚህ እውነተኛ ሃይማኖትን ከጊዜው ስመ መሳይ ኑፋቄና የለየለት ክሕደት ለይቶ በሚያሳይ ትምህርታችን «አበዊነ = አባቶቻችን» ያልናቸው እነማን እንደሆኑ በጥቅል ማመልከት እንወዳለን፡፡ የቃሉን ዐይነ ምስጢር ቁልጭ አድርጎ ለመግለጽ ያህል አባትነት መልክና ይዘቱ፣ ግብርና ዐይነቱ በጣሙን ብዙ ነው፡፡ ይሁንና እዚህ ላይ «የቀናች፣ የጸናች ሃይማኖት» ባለቤቶች ብለን በትምህርታችን ርእስ በመሪነት ያነሣናቸው፡፡
- ከአዳም ጀምሮ እስከ ኖኅ በደብር ቅዱስ የነበሩ አርእስተ አበውን፣
- ከአብርሃም ጀምሮ እስከ ሊቀ ነቢያት ሙሴ የነበሩትን የእግዚአብሔር ሰዎች፣
- አዕይንተ አርጋብ ዐበይት ደቂቅ ነቢያትን፣

የመነኩሳት ሕይወት

ምንም እንኳን የድንግልናና የምናኔ ኑሮ ቀደም ብሎ የተጀመረ ቢሆንም የምንኩስና መሥራችና አባት ቅዱስ እንጦንስ ነው፡፡ አባ እንጦንስ ግብፅ ውስጥ በምትገኝ ቆማ በምትባል ቦታ በ251 ዓ.ም ተወለደ፡፡ ወላጆቹ ሀብታሞችና ደጋግ ሰዎች ነበሩ፡፡ ከወላጆቹ ዕረፍት በኋላ የነበረውን ሀብት ለድሆች መጽውቶ መንኩሶ ብዙ ዓመት በብሕትውና ኖረ፡፡

የእግዚአብሔርን ቅንነት የተረዳ ቅዱስ አባት


ሐምሌ 82003 ዓ.ም
ቅዱስ ኪሮስ ወደ አባ በብኑዳ በደረሰ ጊዜ ዐፅሙ በየቦታው ተበትኖ አንበሳ ሲበላው አገኘ በዚህም ሠዓት በጣም አምርሮ እያለቀሰ “ጌታ ሆይ፥ ለምን እንዲህ ታደርጋለህ ፍርድህ መልካም አይደለም፤ በመንግሥት፥ በመብልና በመጠጥ በደስታ የኖሩትን በክብር እንዲቀበሩ ታደርጋለህ፥ ስለ አንተ ሲሉ አባትና እናትን ሚስትን ልጆችን ደስታን ሁሉ ትተው በተራራና በዋሻ በጾምና በጸሎት የኖሩትን ደግሞ ሥጋቸውን ለዱር አራዊት ትሰጣለህ፥ “የአንተን ፍርድ ነገር ላልሰማ እንዳልነሣ ሕያው ስምህን” ብሎ መሬት ላይ ተኛ፡፡