Monday, October 22, 2012

ዘመነ ጽጌ - ክፍል ሁለት

[ከመስከረም 26 እስከ ኅዳር 6]
"ልጄን ከግብፅ ጠራሁት"   (.ሆሴዕ 111 )
ከመምህር ዮሐንስ  ለማ

እመቤታችን በስደቷ የተጓዘችባቸው
ሐዋርያዊት የሆነች ቅድስት  ቤተ ክርስቲያናችን ከዘመነ ሐዋርያት ጀምሮ ክርስቲያናዊ ትውፊታዋን ጠብቃ፣ መንፈሳዊ አገልግሎቷን በሚገባ አራቅቃ፣ ዘመንን በክፍል በክፍል ቀምራ፤ ከመስከረም ጀምሮ እስከ ጳጉሜን ድረስ ያሉት ሰንበታት የራሳቸው የሆነ ከምሥጢረ ድህነት ጋር የተያያዘ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ስያሜ ሰጥታ የሰው ልጆችን ከመርገመ ሥጋ ከመርገመ ነፍስ ለማዳን የተደረገው (የተፈጸመው) አምላካዊ የድኅነት ጉዞ እያዘከረች፣ እያስተማረች... ለዘመናት ቆይታለች፣ አሁንም በማስተማር ላይ ናት ለወደፊትም እግዚአብሔር እስከ ፈቀደላት ጊዜ ድረስ ስትመሰክርና ስታስተምር ትኖራለች፡፡  እመቤታችን በትልቅ የምስጋና አገልግሎት ከሚከበሩላት በዓላት መካከል የወርሐ ጽጌ (ዘመነ ጽጌ ) አንዱና በሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ልብ ውስጥ ጥልቅ የልቡና ፍቅር ያለው  ይሕ የወርሐ ጽጌ ወቅት  አንዱ ነው ፡፡ በመሆኑም በክፍል አንድ ጽሐፍ   የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያምን ስደት በማስመልከት ምክንያተ ስደቷንና ተያያዥ ርዕሶችን ማስነበባችን  ይታወሳል፡፡ አሁን ደግሞ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም  በስደቷ ወቅት  ያሳለፈቻቸውን  ውጣ ውረድና ተያያዥ ክስተቶችን  እንዲሁም የጉዞዋን ዋና ዋና መዳረሻዎችን ጭምር ለማስነበብ እንሞክራለን፡፡


ዘመነ ጽጌ - ክፍል አንድ

[ከመስከረም 26 እስከ ኅዳር 6]

"ልጄን ከግብፅ ጠራሁት"   (.ሆሴዕ 111 )

ከመምህር ዮሐንስ  ለማ

እንደ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ  ቤተክርስቲያን  ሕግና ስርአት መሰረት ከመስከረም 26 ቀን  እስከ ሕዳር 6 ቀን  ያለው 40 ቀን  የእመቤታችንን እና የልጇን ስደት በማሰብ ወርኃ ጽጌን (ዘመነ ጽጌን) ታከብራለች፡፡ ይህ 40 ቀን የእመቤታችንና የጌታችን ስደት የሚታሰብበት ዘመን ነው፡፡ ወቅቱ የአበባና የፍሬ ወቅት በመሆኑ እመቤታችን በአበባ ጌታችን በፍሬ እየተመሰሉ ጌታችን በአምልኮት እመቤታችን በፈጣሪ እናትነቷ በተለየ ምስጋና ይመሰገናሉ ፡፡

 በስድስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን የተነሳው ታላቁ ሊቅ ቅዱስ ያሬድ አምሥቱን ጸዋትወ ዜማ ሲደርስ 14ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የተነሳው አባ ጊዮርጊስ ደግሞ ሰዓታትን ደርሷል፡፡ በዚሁ ዘመን ከአባ ጊዮርጊስ ጋር ጥልቅ መንፈሳዊ ፍቅር የነበረው አባ ጽጌ ድንግል  ማኅሌተ ጽጌ  የተባለውን ድርሰት ደርሷል፡፡  ማኅሌተ ጽጌ ግጥማዊ አካሄድ ያለው ድንቅ ኢትዮጵያዊ ድርሰት ሲሆን  ይህ ድርሰት በማንኛውም ጊዜ የሚጸለይ ቢሆንም በተለየ ሁኔታ ወቅት ተለይቶለት በቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ላይ የሚውለው ግን   በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምና በልጇ የስደት ዘመን  ማለትም  ከመስከረም 26 እስከ ኅዳር 5 ቀን ድረስ ባለው  ዘመን ውስጥ ነው፡፡ በዚህ ወቅት በየሳምንቱ እሑድ ሌሊቱን በሙሉ የእመቤታችንን ከልጇ ጋር ወደ  ምድረ ግብፅ መሰደድና መንከራተት እየታሰበ በሊቃውንቱ  የሚደርስ የምሥጋና ጸሎትም  ነው ፡፡ ይህ ድርሰት በግጥም መልክ የተደረሰ  ሲሆን በአብዛኛው አምስት ስንኞች ሲኖሩት ብዛቱም 158 ያክል ነው፡፡ እመቤታችን ጣዕሟንና ፍቅሯን እንዲሁም ምስጋናዋን ሲናፍቁ የነበሩትን ቅዱስ ኤፍሬምንና አባ ሕርያቆስን ውዳሴዋንና ቅዳሴዋን እንደገለጸችላቸው  ሁሉ ለፍቅሯ ሲሳሳ ለነበረው ለአባ ጽጌ ድንግል ደግሞ ይህንን የማኅሌተ ጽጌን ድርሰት  እንዲደርስ ምስጢርን ገልጻለታልች

ሕፃኑንና እናቱን ይዘህ ወደ ግብጽ ሽሽ


   በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
የዚህ ትምህርት መሠረታዊ ዓላማ ክርስቲያኖች ከጌታችንና ከእመቤታችን ስደት በረከት ተሳታፊዎች እንዲሆኑ ማድረግ ነው፡፡
  ቀዳማዊ አዳም የማይበላ በልቶ በራሱና በልጆቹ የሞት ሞት ተፈረደበት፤ ጸጋ እግዚአብሔር ጎደለበት፤ የሚሠዋው መሥዋዕት የሚጸልየው ጸሎት ግዳጅ የማይፈጽም ሆነበት፡፡ ምድር ከእርሱ የተነሣ እሾክና አሜከላ አበቀለችበት፡፡

  ሆኖም (አዳም) ምንም ባልበደለው ሰይጣን እንዲሁ ቢሞትም የተበደለው አምላኩ ግን እንዲሁ ሕይወትን ይሰጠው ዘንድ ወደደ፡፡ (አዳም) አምላክ መሆንን ሽቶ ነበርና ይህን ይሰጠው ዘንድ (አምላክ) ዳግማይ አዳም ይሆንለት ዘንድ ወደደ፤ አስቀድሞ ከነበረው ክብር በላይ ሌላ ክብር ይጨምርለት ዘንድ ፈቀደ፡፡ ጊዜው ሲደርስም አካላዊ ቃል ንጹሕ የሆነ ባሕርዩን (የእመቤታችን ሥጋና ነፍስ) ነሥቶ ዝቅ ያለውን ከፍ ያደርገው ዘንድ ዝቅ አለለት፤ የጸጋ ልብሱን ይመልስለት ዘንድ የማይዳሰስ እርሱ በጨርቅ ተጠቀለለት፤ ወደ ክብሩ ይመልሰው ዘንድ በርካሽ ቦታ ያውም በግርግም ተወለደለት፡፡ 

ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን
 ባለፈው ዝግጅታችን ስለቅዱሳን ሐዋርያት አጠቃላይ መግቢያ አቅርበን በቀጣይነትደግሞ እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ የእያንዳንዱን ሐዋርያ የተጋድሎ ሕይወት በዝርዝርእንደምናቀርብ ቃል ገብተን ነበር (የባለፈውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ-http://mekrez.blogspot.com/2012/09/blog-post_12.html) በመሆኑም ለዛሬየሐዋርያት አለቃ የሆነውን የሐዋርያው የቅዱስ ጴጥሮስን ሕይወትና ተጋድሎ እነሆብለናል መልካም ንባብ።

 ቅዱስ ጴጥሮስ የተወለደው በገሊላ ባሕር ዳርቻ ( የገሊላ ባሕር ስያሜዎችአሉት፡- () የገሊላ ባሕር (በገሊላ አውራጃ ስለሚገኝ) በዙሪያው ባሉ ጌንሴሬጥናጥብርያዶስ በሚባሉ ከተሞች ስም ደግሞ () ባሕረ ጌንሴሬጥ እና () ባሕረጥብርያዶስ ይባላል) ባለች ቤተሳይዳ በተባለች ከተማ ውስጥ ነው የአባቱ ስም ዮናሲሆን ትውልዱም ከነገደ ሮቤል ነው። እናቱ ደግሞ ከነገደ ስምዖን ወገን የሆነችነበረች።  በመሆኑም እንደ ኦሪት ሥርዐት ስም ሲያወጡለት በእናቱ ነገድ ስምስምዖን ብለውታል። አባቱ ዮና የያዕቆብና የዮሐንስ አባት ከሆነው ከዘብዴዎስ ጋርየሥራ ባልንጀራ ሲሆን የሁለቱም  ሥራቸው ዓሣ እያጠመዱ መሸጥ ነበር። እድሜው፭ ዓመት ሲሆን ኦሪትን እየተማረ እንዲያድግ በአቅራቢያቸው ወዳለ ወደቅፍርናሆም ምኩራብ ሰደዱት። ቅዱስ ጴጥሮስ በቅፍርናሆም እየተማረ ካደገ በኋላበዚያው ቤት ሠርቶ ኮንኮርድያ (ጴርጴቱዋየምትባል ሚስት አግብቶ እንደ አባቱዓሣ እያጠመደ በመሸጥ መኖር ጀመረ።