Wednesday, April 25, 2012

ትንሣኤ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አምላክ! አሜን!
“… ሕያውን ከሙታን መካከል ስለምን ትፈልጋላችሁ? ተነሥቶአል እንጂ በዚህ የለም ።ሉቃስ ፳፬ ÷
ያለውናየነበረው የሚመጣውም ከሙታንም በኵርሆኖ የተነሣው በምድርና በሰማያትያሉትን ሁሉ የሚገዛ የነፍሳችንቤዛና እረኛ በርኅራኄው ብዛትየወደደን፣ ከኃጢአታችንም በከበረ ደሙያጠበን ቅዱሱ የማርያም ልጅከባሕርይ አባቱ ከአብ፣ ከባሕርይሕይወቱ ከመንፈስ ቅዱስ ጋርለዘለዓለም የተመሰገነ ይሁን! አሜን!
ተሳስተንበሠራነው ኃጢአት፣ በበደላችንም ምክንያትእንደ ደረቀ ቅጠል ከመርገምናከሞት ስር ወድቀን፣ ጽድቃችንእንደመርገም ጨርቅ ሆኖ ሳለቃልኪዳኑን የማይረሳ አምላክ ከሰማያትተመለከተ። ከአቤል ጀምሮ የፈሰሰውየቅዱሳን ደም፣ ከአዳም ጀምሮየቀረበው የኃጢአት መስዋዕት የአዳምንልጅ ሊያድነው እንዳልቻለ አየ።አዳምና ልጆቹ ለብዙ ዘመናትበመንፀፈ ደይን ድቀው፤በዲያቢሎስ የባርነት ቀንበር ተይዘውበሲኦልና በግዞት መሰቃየታቸውንና ወደቀደመውርስት ለመመለስ መናፈቃቸውን አስተዋለ።ስለዚህም ከቅዱስነቱና ከክብሩ ማደሪያከጽዮን ጎበኘን።
እነሆ!የዘመኑ ፍፃሜ በደረሰ ጊዜ፣ለፍጥረቱ የሚገደው ጌታ እግዚአብሔርየመከራና የጭንቀት ቀናትን፣ የጉስቁልናናየሥቃይ፣ የጨለማና የጭጋግ ደመና ዘመናትን ያሳልፍ ዘንድ፤የተዋረደውን ሊያከብር፣ የወደቀውን ሊያነሣ፣የሞተውንም ሕይወት ይሰጥ ዘንድ፤በቸርነቱና በፍቅሩ በትህትናውም ብዛትሥጋን ለበሰ። መለኮት የሥጋንባሕርይ ገንዘብ አደረገ፣ የፈጠረውንምሥጋ ተዋሐደ። ከኃጢአትም በቀርፍፁም ሰው ሆነ። የንጋትኮከብ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስሁለተኛ ሰማይ ከሆነችው ከድንግልማርያም ተወለደ፤ የጽድቅ ፀሐይአምላክ፣ ከእውነተኛዋ ምሥራቅ ከብርሃንእናት ከድንግል ወጣ፤ በመላውዓለምም አበራ። የማይታየው ታየ፣ዘመን ዕድሜ የማይቆጠርለት ዘመንተቆጠረለት።
ዘመኑም በዕደ ዮሐንስ ተጠመቀ፤ በገዳመ ቆሮንቶስ ፵ መዓልትና ፵ ሌሊት ጾመ፤ ፈታኙንም ድል አደረገ። “ዘመኑ ተፈጸመ፤ የእግዚአብሔርም መንግሥት ቀርባለች፤ ንስሐ ግቡ፤ በወንጌልም እመኑ።” እያለ ወደገሊላ መጣ። ማርቆስ ፩÷፲፭ወንጌልን በእስራኤል አውራጃዎች ሰበከ፤በፊታቸውም ብዙ ድንቅና ተአምራትንአደረገ፤ ሕሙማንን ፈወሰ፣ ለምጻሞችንአነጻ፣ የዕውራንን ዓይን አበራ፣አንካሶች እንዲሄዱ ደንቆሮዎች እንዲሰሙ አደረገ፣ሙታንን አስነሣ። ለሰማያዊ መንግስትናለዘላለማዊ ሕይወት የሚያበቃውን የቤዛነትንቃል አስተማረ። ጥቂቶች በቃሉተመሩ፤ ብዙዎች ግን ሊያድናቸውናሊታደጋቸው ወደ አባቱም መንግሥትሊያፈልሳቸው እንደመጣ አላወቁም። ይልቁንምየአይሁድ አለቆችና ካህናት አብዝተውይቃወሙት ሊገድሉትም ያሴሩ ነበር።በምሴተ ሐሙስ እራት ከበሉበኋላ ቁጥሩና ዕድል ፈንታውከሐዋርያት ጋር የነበረው ይሁዳጌታን በመሳም ለአይሁድ አለቆችአሳልፎ ሰጠ። መስፍኑ ጲላጦስጌታ ከተከሰሰበት ጉዳይ አንዳችእውነት ባላገኘ ጊዜ ሊፈታውወደደ። የካህናት አለቆች ግንሕዝቡን አሳምፀው እንዲሰቀል ግድአሉት። ጌታም በሐሰት ፍርድለሞት ተላልፎ ተሰጠ። በመስቀልምቸነከሩት፣ እርሱ ግን የፍቅርአምላክ ነውና በመስቀል ላይሆኖም የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው በማለትቸርነቱን ገለጠላቸው። በእርሱ ቁስልእንድንፈወስ፣ በሕማሙ ድኅነት እንዲሆንልን፤ በሞቱ ሕይወትን እንድናገኝ፣በፈቃዱ ታመመ፣ መከራን ተቀበለእንጂ የሰው ልጅ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ላይ ምንም ነገርማድረግ አይቻለውም ነበር። ጌታችንናመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሙታንንያድን ዘንድ ሞተ፣ የሞትንናየዲያብሎስን ኃይል በሥልጣኑ ሽሮበሰንበት ከሙታን ተለይቶ ተነሣ፤ክብርና ምሥጋና ለእርሱ ይሁን!አሜን!

Monday, April 16, 2012

እንኳን ለጌታችን እና መድኅኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ትንሳኤ በሰላም አደረሰን

ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን፤ በዐቢይ ኃይል ወሥልጣን፤ አሰሮ ለሰይጣን፤ አግዐዞ ለአዳም፤ ሠላም እምይዕዜሰ፤ ኮነ፤ ፍስሐ ወሠላም፡፡"
በመ/ር ምሥጢረ ሥላሴ ማናየ

“ክርስቶስ በታላቅ ኃይልና ሥልጣን ከሙታን ተለይቶ ተነሣ ዲያብሎስን አሰረው አዳምን ነጻ አወጣው ሠላም ከዛሬ ጀምሮ ሰላም ሆነ” ይህ ቃል የትንሣኤው የምሥራች ለምእመናን የሚታወቅበት ነው የሚቀድስ ካህን፣ ሰባኪ በዘመነ ትንሣኤ ከስብከቱ አስቀድሞ በዚህ ቃል የክርስቶስን መነሣት ያውጃል፡፡ የሚቀድሰው ካህንም በኪዳን ጊዜ ህዝቡን ከመባረኩ አስቀድሞ ይህንኑ ቃል ይናገራል ሰላምታ የሚቀባበሉ ምእመናንም ሰላምታ ከመስጠት አስቀድሞ ይህን ቃል በመናገር የትንሣኤውን አዋጅ ማወጅና መመስከር ይገባቸዋል፡፡ እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው አደረሰን አደረሳችሁ፡፡

የክርስቶስ ትንሣኤ እንደ እንግዳ ደራሽ እንደ ውኃ ፈሳሽ አይደለም ከጥንት በነቢያት የተነገረ ኋላም እርሱ ክርስቶስ ለደቀ መዛሙርቱ ከመሞቱ አስቀድሞ ያስተማረው ደግሞም በመነሣት የገለጠው ሐዋርያትም በግልጥ ለዓለም የመሰከሩት ነው፡፡

ትንሣኤ በትንቢተ ነቢያት

“እግዚአብሔር ይነሣል ጠላቶቹም ይበተናሉ” “እግዚአብሔር ከእንቅልፍ እንደሚነቃ ተነሣ የወይን ስካር እንደተወው እንደ ኃያልም ሰው ጠላቶቹንም በኋላው መታ” መዝ.77፥6 “እኔ ተኛሁ አንቀላፋሁም እግዚአብሔር አሥነስቶኛልና ተነሣሁ” መዝ.3፥5 “እግዚአብሔር አሁን እነሣለሁ ይላል መድኀኒት አደርጋለሁ

Thursday, April 12, 2012

ጸሎተ ሐሙስ


ነቢያት በሀብተ ትንቢት በመንፈሰ ትንቢት ‹‹እግዚአብሔር የሠራት ቀን ይህች ናት›› /መዝ. 117፥24/ በማለት ትንቢት የተናገሩላት በቤተ ክርስቲያናችን አስተምህሮ ትላልቅ የተባሉ ምሥጢራት የተፈጸሙባት ዕለት ናት፡፡

“እግዚአብሔርም በግብጽ አገር ሙሴንና አሮንን እንዲህ ብሎ ተናገራቸው ይህ ወር የወሮች የመጀመሪያ ይሁናችሁ የዓመቱም የመጀመሪያ ወር ይሁናችሁ፡፡ ለእስራኤል  ልጆች ሁሉ ተናገሩ፥ በሉአቸውም በዚህ ወር በአሥረኛው ቀን ሰው ሁሉ ለአባቱ ቤት አንድ ጠቦት ለአንድ ቤትም አንድ ጠቦት ይውሰድ፡፡ የቤቱ ሰዎች ቁጥርም ለጠቦቱ የማይበቃ ቢሆን እርሱና ለቤቱ የቀረበው ጎረቤቱ እንደነፍሶቻቸው ቁጥር አንድ ጠቦት ይውሰድ እያንዳንዱም እንደሚበላው መጠን ከጠቦቱ ይካፈሉ፡፡ የእናንተ ጠቦት ነውር የሌለበት የአንድ ዓመት ተባት ይሁን ከበጎች ወይም ከፍየሎች ውሰዱ በዚህም ወር እስከ አሥራ አራተኛ ቀን ድረስ ጠብቁት፡፡ የእስራኤልም ጉባኤ ሁሉ ሲመሽ ይረዱት፡፡ ከደሙም ወስደው በሚበሉበት ቤት ሁለቱን መቃንና ጉበኑን ይቀቡት፡፡ በእሳት የተጠበሰውን ሥጋውንና ቂጣውን እንጀራ በዚያች ሌሊት ይብሉ ከመራራው ቅጠል ጋር ይበሉታል ጥሬውን በውኃ የበሰለውን አትብሉ ነገር ግን ከራሱ ከጭኑ ከሆድ ዕቃው ጋር በእሳት የተጠበሰውን ብሉት ከእርሱም እስከ ጧት አንዳች አታስቀሩ እስከ ጧትም የቀረውን በእሳት አቃጥሉት ወገቦቻችሁን ታጥቃችሁ፥ ጫማችሁን በእግራችሁ በትራችሁንም በእጃችሁ አድርጋችሁ እንዲህ ብሉት፡፡ ፈጥናችሁም ትበሉታላችሁ እርሱ የእግዚአብሔር ፋሲካ ነው፡፡ እኔም በዚያች ሌሊት በግብጽ አገር አልፋለሁ… ይህም ቀን መታሰቢያ ይሁንላችሁ፥ ለእግዚአብሔርም በዓል ታደርጉታላችሁ ለልጅ ልጃችሁም ሥርዓት ሆኖ ለዘላለም ታደርጉታላችሁ /ዘዳ.12፥1-15/፡፡
እስራኤል ይኸንን ሥርዓት በሚፈጽሙበት ዓመታዊ በዓል ዋዜማ ላይ ነበር ሐዋርያቱ ወደ ጌታችን ቀርበው እንዲህ ያሉት “ፋሲካን ትበላ ዘንድ ወዴት ልናሰናዳልህ ትወዳለህ?  እርሱም ወደከተማ ወደ አልዓዛር ቤት ላካቸው /ማቴ.20፥6-18/፡፡ አስቀድመን የገለጥነው ቃል እስራኤል ዘሥጋ ከሞተ በኩር የዳኑበት የፋሲካ በግ ምሳሌነት የሚያሳይ ነው፡፡
በጉ ነውር የሌለበት የመሆኑ ምክንያት ኀጢአት የሌለበት የጌታችን ምሳሌ ነው፡፡ በጉን በወሩ በዐሥራ አራተኛው ቀን እንዲሠውት እንደታዘዙ የጌታ ምክረ ሞቱ በዐሥር ተጀምሮ በዐሥራ አራተኛው ቀን ተፈጽሟል፡፡ የበጉ ደም የተቀባበት ቤት ሞተ በኩር አልደረሰም በመስቀሉ ላይ የፈሰሰውን ቅዱስ ሥጋውን ክቡር ደሙን የሚቀበሉ ክርስቲያኖችንም ሞት አይደርስባቸውም፡፡ የበጉን ሥጋ ጥሬውንና ቅቅሉን እንዳይበሉ ጥብሱን እንዲበሉ  ታዘዋል ይህም በእሳት የተመሰለ መለኮት የተዋሐደውን ነፍስ የተለየውን ሥጋና ደም ለምንቀበል ለእኛ ማስተማሪያ ይሆን ዘንድ ነው፡፡

ሰሞነ ሕማማት (ማክሰኞ)

በዚህ ዕለት ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱሱ ክርስቶስ ስለ ሥልጣኑ ተጠይቋል፡፡ ጠያቂዎቹ የካህናት አለቆችና የሕዝብ አለቆች ናቸው፡፡ ጥያቄውም “በማን ሥልጣን እነዚህን ታደርጋለህ? ይህንስ ሥልጣን የሰጠህ ማነው?” የሚል ነበር፡፡ የካህናት አለቆች ያቀረቡት ጥያቄ ነበር፡፡ ጌታችን ሰኞ ዕለት ሁለት ነገሮችን ማድረጉን ተያይዞ የተነሣ ጥያቄ ነው፡፡ ሰኞ ከቅጠል ብቻ በቀር ፍሬ ያላገኘባትን ዕፀ በለስ ረግሟል፤ በማስከተል ወደ ቤተ መቅደስ ገብቶ የሚሸጡትንና የሚለውጡትን አስወጥቷል፡፡ ማቴ.21÷23-25፤ ማር.11÷27፣ ሉቃ.20÷1-8፡፡ ከላይ እንደ ተገለጸው ጌታችን ሲያደርጋቸው የነበሩት ተአምራትና የኃይል ሥራዎች የካህናት አለቆችን ስላስቀናቸው ጌታችንን ከሮማ መንግሥት ባለ ሥልጣናት ጋር ለማጋጨት የቀየሱት ስልት ነው፡፡

ጌታችን በቤተ መቅደስ የነበሩትን ነጋዴዎችን አባሯል፤ መደባቸውን ገለባብጧል፡፡ ነጋዴን ማባረርና መደብን ማስለቀቅ መንግሥታዊ ሥራ ነው፡፡ በአንድ አገር የንግድ ቦታን የሚያጸድቅ መንግሥት መሆኑ እሙን ነው፡፡ ጌታችን ፈሪሳውያን ላቀረቡት ጥያቄ ቀጥተኛ መልስ አልመለሰም፡፡ ምክንያቱም ጥያቄው ለከሳሾቹ አመቺ ሁኔታን ስለሚፈጥር ጥያቄውን በጥያቄ መልሷል፡፡ “በመባሕተ መኑ ትገብር ዘንተ፤ በማን ሥልጣን ነው ይህን የምታደርገው?” ነበር ያሉት፡፡ በራሴ ሥልጣን ቢላቸው ፀረ መንግሥት አቋም አለው በማለት ከሮማ መንግሥት ዘንድ ለማሳጣት ነበር ዕቅዳቸው፡፡
ጌታችን እኩይ የሆነውን የፈሪሳውያንን አሳብ በመረዳት “የዮሐንስ ጥምቀት ከየት ነው ከሰማይ ነው ወይስ ከምድር ሲል” ጠይቋቸዋል፡፡ ከሰማይ ያልነው እንደ ሆነ ለምን አላመናችሁበትም ይለናል÷ ከሰው ያልነው ከሆነ ሕዝቡ ይጣላናል፡፡ ምክንያቱም ሕዝቡ ዮሐንስን እንደ አባት ይፈሩት እንደ መምህር ያከብሩት ነበርና ከዚህ የተነሣ ያቀረቡት የፈተና ጥያቄ ግቡን ሳይመታ ከሽፎባቸዋል፡፡ ማቴ.21÷25፤ ማር.11÷27-30፤   ሉቃ.20÷1-8፡፡
ዛሬም ቢሆን መልካም ሥራን በሠራን ጊዜ ከልዩ ልዩ ወገኖች የሚመጡ ፈተናዎች ለመልካም ሥራችን እንቅፋት ሊሆን እንደሚችሉ መገንዘብ አለብን፡፡ ብዙ ወገኖች ለቅን አሳባችን ለምን ሰዎች ክፉ ነገር ይመልሱልናል በማለት ሲጠይቁ ይሰማል፡፡ ለቅን ዐሳባችን ከዓለም ዘንድ የተገላቢጦሽ ነገር እንደ ሚጠብቀን “ዓለም የሚወደው የገዛ ወገኑን ነው” የሚለውን የጌታችንን ትምህርት ልብ ይሏል፡፡ ይህ በመሆኑ በዘመናችን አሳልፈው ሊሰጡን የሚፈልጉ ሰዎች ፈታኝ ጥያቄ እንደሚያቀርቡልን ከወዲሁ ልንገነዘብ ይገባል፡፡
ምንጭ የማኅበረ ቅዱሳን ድረ ገጽ  ነው::

ሰሙነ ሕማማት /ሰኞ

ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ከትንሣኤ በፊት ያለውን አንድ ሳምንት ሰሙነ ሕማማት /የሕማማት ሳምንት/ በማለት ትዘክረዋለች፡፡ ሕማማት የሚለው ቃል “ሐመ፤ ታመመ” ከሚለው የግእዝ ግስ የወጣ ሲሆን የጌታችንና የመድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሕማምና ሞቱ የሚዘከርበት ሳምንት ነው፡፡ በሌላም በኩል ይህ ሳምንት ከአዳም እስከ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱሱ ክርስቶስ የነበሩ ነፍሳት በሲኦል የቆዩበት የአምስት ሺህ አምስት መቶ የመከራ፣ የፍዳና የኩነኔ ዘመን መታሰቢያ ስለሆነ የሕማማት ሳምንት የሚለውን ስያሜ አግኝቷል፡፡ እንደዚሁም ይህ ሳምንት “ቅዱስ ሳምንት” ይባላል” ከሌሎች ሳምንቶች ሁሉ የተለየ የከበረ ነውና፡፡ ምክንያቱም በዚህ ሳምንት በእያንዳንዱ ዕለት ስለ ፍጹም ፍቅር የተከፈለ የመሥዋዕትነት ሥራ ስለ ተሠራበት፣ የሰው ልጆች ደኅንነት ስለ ተፈጸመበት፣ መድኀኔዓለም ስለ እኛ ቤዛ ሆኖ ለመስቀል ሞት ታዛዥ ሆኖ ነፍሱን ስለ ካሠልን “ቅዱስ ሳምንት” ተብሏል፡፡ በተጨማሪም “የመጨረሻ ሳምንት” ተብሎ ይጠራል፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዚህ ዓለም በሙዓለ ሥጋዌው ለፈጸማቸው የቤዛነትና የአርአያነት ተግባራት ፍጻሜ በመሆኑ ነው፡፡
በዚህ ልዩ በሆነ ሳምንት ካህናትና ምእመናን በነግህ፣ በሠልስት፣ በቀትር፣ በተሰዓትና በሠርክ ወደ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በመጓዝ ስለ ጌታችን ኢየስስ ክርስቶስ ሕማማተ መስቀል የሚያዘክረውን ምዕራፍ ከቅዱሳት መጻሕፍት በማንበብና በመጸለይ ሕማሙንና ሞቱን ያዘክራሉ፤ ቅዱስ ያሬድ በመጨረሻው ሳምንት በየዕለቱ በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ላይ የተፈጸመውን ነገረ መስቀል በተመለከተ ያዘጋጀውን መዝሙር ይዘምራሉ፤ አብዝተው ስግደትን ይሰግዳሉ፡፡

Sunday, April 1, 2012

"የበገና አገልግሎት በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን"


"የበገና አገልግሎት በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን"

በገና የኢትዮጵያ /ክርስቲያን የምስጋና መሳሪያ

በገና 
"በገና"- እንደሌሎች የሃገራችን ጥልቅ ብሔራዊ የታሪክ ሃብቶችና በታሪክም ከእስራኤል ቀጥሎየኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ብቸኛ ጥንታዊ የዜማ መሣርያ ጥንታዊ ይዘቱን የጠበቀ የሀገር ሀብት እንደመሆኑ መጠን ሁለት ዓይነት ትርጉም አለው፡፡
እነርሱም፡-
1. ሰዋስዋዊ ትርጉምና
2. ሥነ ቃላዊ ትርጉም.............. ይባላሉ፡፡
1. የበገና ሰዋስዋዊ ትርጉም
"በገና" የሚለው ስምና "በገነ" የሚለው ግሥ በተለያዩ መዝገበ ቃላትና የቋንቋ ሊቃውንት ተተርጉሞእናገኛለን፡፡ ለምሳሌ፡- አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ"መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ መዝገበ ቃላት ሐዲስ"በሚል መጽሐፋቸው በሁለት መልኩ ማለት "ሲጠቅብና ሲላላ" ብለው በማመሳጠር እንዲህብለውተርጉመውታል፡፡
በገና - በዕብራይስጥ ናጌን ይባላል ካሉ በኋላ ሲተረጉሙት - ነዘረ፣ መታ፣ ደረደረ፣ ማለትነው፡፡ ሲጠብቅ ግን - ነደደ፣ ተቆጣ... ያሰኛል ብሏል፡፡
በገና፡ - በቁሙ መዝሙር ማለት ነው ብለውም ፈትተውታል፡፡ (አለቃ ኪዳነ ወልደ ክፍሌ፡መጽሐፈ ስዋስው ወግስ ወመዝገበ ቃላት ሐዲስ)