| |
በመ/ር ኃይለማርያም ላቀው
የጋብቻ ሕይወት በኤደን ገነት እንደተጀመረ ይታወቃል፡፡ ዘፍ 2÷26 በዘመነ ሐዲስም መርዓዊ ሰማያዊ ክርስቶስ በቃና ዘገሊላ ከእመቤታችን ጋር ተገኝቶ የዶኪማስን ጋብቻ ባርኳል ፣ ቀድሷል፡፡ ዮሐ 2÷1-10፡፡ቅድስት ቤተ ክርስቲያንም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በቃና ዘገሊላ ጋብቻን መባረኩን፣ ዓለምን ለማስተማር መገለጡን ለማዘከር ከጥር መባቻ እስከ ዐቢይ ጾም መግቢያ ያለውን ወቅት ‹‹ዘመነ መርዓዊ›› በማለት ትጠራዋለች፡፡ በመሆኑም በዚህ ወቅት በኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ጸንተው ፣በድንግልና ራሳቸውን ጠብቀው ለኖሩ ሥርዓተ ተክሊልን በመፈጸም አንድ ታደርጋቸዋለች፡፡
እንዲሁም በሥጋዊ ድካም ድንግልናቸውን ሳይጠብቁ ለኖሩ ልጆቿ ከንስሐ በኋላ ለመዓስባን የሚደርሰውን ጸሎት አድርሳ ሥርዓተ ጋብቻን ትፈጽምላቸዋለች፡፡
|


የጋብቻ ሕይወት በኤደን ገነት እንደተጀመረ ይታወቃል፡፡ ዘፍ 2÷26 በዘመነ ሐዲስም መርዓዊ ሰማያዊ ክርስቶስ በቃና ዘገሊላ ከእመቤታችን ጋር ተገኝቶ የዶኪማስን ጋብቻ ባርኳል ፣ ቀድሷል፡፡ ዮሐ 2÷1-10፡፡ቅድስት ቤተ ክርስቲያንም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በቃና ዘገሊላ ጋብቻን መባረኩን፣ ዓለምን ለማስተማር መገለጡን ለማዘከር ከጥር መባቻ እስከ ዐቢይ ጾም መግቢያ ያለውን ወቅት ‹‹ዘመነ መርዓዊ›› በማለት ትጠራዋለች፡፡ በመሆኑም በዚህ ወቅት በኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ጸንተው ፣በድንግልና ራሳቸውን ጠብቀው ለኖሩ ሥርዓተ ተክሊልን በመፈጸም አንድ ታደርጋቸዋለች፡፡





